- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን ነባር ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ ጥቅምት 23-24/2014 ዓ/ም የሚካሄድ ሲሆን ትምህርት የሚጀመረው ጥቅምት 29/2014 ዓ/ም ይሆናል፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም ነባር ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ፡-
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና “Christian Aid” የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት በኢኖቬቲቭ እንሰት ፕሮጀክት የተሠሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንሰት አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለማዳረስ መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡ ከድርጅቱ የመጡ የሥራ ኃላፊዎች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በመሆን ጥቅምት 9/2014 ዓ/ም በዶርዜና ግርጫ ምርምር ማዕከላት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በቅርቡም የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ተግባር እንደሚገባ ታውቋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በኢኖቬቲቭ እንሰት ፕሮጀክት የተሠሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንሰት አብቃይ ለሆኑ አካባቢዎች ለማዳረስ የጋራ ውይይት ተካሄደ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አውስትራሊያ ሀገር ከሚገኘው “Menzies School of Health Research” ከተሰኘ የጤና ምርምር ት/ቤት ጋር ‹‹Effectiveness of Novel Approaches to Radical Cure of Vivax Malaria with Tafenoquine and Primaquine›› በሚል ርዕስ 210 ሺህ ዶላር የተመደበለት ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት ለማከናወን ጥቅምት 5/2014 ዓ/ም የመግባቢያ ስምምነት በቨርችዋል ተፈራርመዋል፡፡
Read more: የወባ በሽታ መድኃኒቶች ውጤታማነትን ለመፈተሽ ለሚከናወነው የምርምር ፕሮጀክት የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ
- Details
የዩኒቨርሲቲው ሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ከአርባ ምንጭ ከተማ ለተወጣጡ በኤችአይቪ/ኤድስ ለተጎዱና አቅም ለሌላቸው 200 ተማሪዎች ጥቅምት 2/2014 ዓ/ም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም 2ኛውን ዓለም አቀፍ የኦሞቲክ ቋንቋ ዓውደ ጥናት ከጥቅምት 01-02/2014 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ በዓውደ ጥናቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት በኦሞቲክ ቋንቋ ላይ የተሠሩ 17 ጥናቶች ቀርበው የቋንቋው ተናጋሪዎች ባሉበት ተገምግመዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ