
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበትን 13ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከፌዴራል፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ከልል እና ከጋሞ ዞን አስተዳደር የህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር ‹‹በኅብረት ችለናል›› በሚል መሪ ቃል የአባይ ዘመን ትውልድ የሥነ ጽሑፍ ምሽት ግንቦት 13/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአባይ ዘመን ትውልድ ታላቅ የሥነ ጽሑፍ ምሽት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ት/ክፍል በ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› የትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው የዕጩ ዶ/ር ኢያሱ ጫማ የመመረቂያ ጽሑፍ ግንቦት 13/2016 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉ አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላቱ በአማካሪ ቦርዱ ጸድቋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
ዕጩ ዶ/ር ኢያሱ ጫማ የመጀመሪያ ዲግሪውን በ‹‹Biology›› እና ሁለተኛ ዲግሪውን በ‹‹Dryland Biodiversity›› ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝቷል፡፡ የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› በ2010 ዓ/ም የጀመረው ዕጩ ዶ/ር ኢያሱ የመመረቂያ ምርምሩን ‹‹Plant Communities, Socioeconomic Values, and Carbon Stock Potential of Forest Patches in Wolaita, Southern Ethiopia›› በሚል ርዕስ አከናውኗል፡፡
ዶ/ር ገመዶ ዳሎ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዶ/ር ዳንኤል ፍታሞ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመመረቂያ ጽሑፍ የውጪ ገምጋሚ ሲሆኑ ዶ/ር ሽቴ ጋተው ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ገምጋሚ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ በግምገማ መርሃ ግብሩ የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎችን ጨምሮ የኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የዘርፉ መምህራንና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ታድመዋል፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCAD/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ አዘጋጅነት ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አራት ወረዳዎች የመጡ የባሕል መድኃኒት አዋቂዎች፣ የግብርና ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች በተገኙበት ግንቦት 9/2016 ዓ/ም የግራንድ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በባሕላዊ መድኃኒቶች ላይ ያተኮረ ግራንድ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ወርክሾፕ ተካሄደ

- Details
የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ እና ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ጋር በመተባበር በዝሆኔ ወይም የእግር እብጠት/Elephantiasis/ በሽታ ዙሪያ ከግንቦት 12-14/2016 ዓ/ም ከክልሉ ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በሽታው በብዛት ከሚከሰትባቸው ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በተከታታይ ሰባት ዙሮች እንደ ቦታው ቅርበት በክላስተር ተከፋፍሎ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ዝሆኔ/Elephantiasis/ በሽታን አስመልክቶ ለጤና ባለሙያዎች ሥልጠና ተሰጠ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብ ኮሌጅ የምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ‹‹Improving the English Language Literacy Skills Performance of English Language Teachers through Flipped Phonics Training፡ The Case of Some Selected Primary Schools of Gamo Zone,Ethiopia›› በሚል ርእስ የአንደኛ ደረጃ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራን የንባብና ጽሕፈት ችሎታ ማሻሻያ ላይ ጥናት ለማስጀመር ግንቦት 10/2016 ዓ/ም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ ጥናቱ በጋሞ ዞን ባሉ ምዕራብ ዓባያ፣ ጨንቻ፣ አርባ ምንጭ ዙሪያና ገረሴ ወረዳዎች እና ብርብርና ገረሴ ከተሞች ከ12-18 ትምህርት ቤቶችን የሚያካልል ሲሆን በአጠቃላይ 60 መምህራን ሥልጠናውን የሚያገኙ ይሆናል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአንደኛ ደረጃ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራን የንባብና ጽሕፈት ችሎታ ማሻሻያ ላይ ጥናት ለማስጀመር ውይይት ተካሄደ