
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከድሪም ፎር ዴቨሎፕመንት ድርጅት/Dream for Development International Ethiopia/ እና ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር ‹‹ምርጫ ለሀገር ህልውና ግዴታ ነው ወይስ አይደለም?›› በሚል ርእስ ግንቦት 22/2016 ዓ/ም በት/ቤቱ ተማሪዎች መካከል ክርክር አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ምርጫ እና የሀገር ህልውናን አስመልክቶ በሕግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች መካከል ክርክር ተካሄደ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹RUNRES - The Rural-Urban Nexus፡ Establishing Nutrients Loop to Improve City Region Food System Resilience Project›› ምዕራፍ አንድ ማብቂያና ምዕራፍ ሁለት ማስጀመሪያ ውይይት ግንቦት 22/2016 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የ‹‹RUNRES Project›› ምዕራፍ አንድ ማብቂያና የምዕራፍ ሁለት ማስጀመሪያ ውይይት ተካሄደ

- Details
የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዲስ በሚከፈተው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለሚያገለግሉ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን እና በአምስቱ ካምፓሶች ለሚገኙ የተማሪዎች አገልግሎት ክሊኒክ የጤና ባለሙያዎች በኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር (Infection Preventing and Controlling) ዙሪያ ከግንቦት 13-24/2016 ዓ/ም በሁለት ዙሮች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲው ጤና ባለሙያዎች ሥልጠና ተሰጠ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከኮሌጁ የተለያዩ ት/ክፍሎች ለተወጣጡ መምህራን እንዲሁም ከአርባ ምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ለመጡ ባለሙያዎች ‹‹Statistical Data Management and Analysis›› በሚል ርእስ የምርምር ሥራ ደጋፊ ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከግንቦት 14-17/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡