- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስዊዘርላንድ ሀገር ከሚገኘው ኢት-ዙሪች/ETH-Zurich/ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ገጠርንና ከተማን በንጥረ ነገር ዕሴት ሠንሰለት በሚያስተሳስር “RUNRES/ረንረስ” በተሰኘ ፕሮጀክት በአርባ ምንጭ ከተማና ዙሪያዋ ባሉት የገጠር ቀበሌያት ላይ የተለያዩ ተግባራትን ሲሠራ ቆይቶ የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ በመጠናቀቁ የሥራዎቹን አፈጻጸም እና የፕሮጀክቱን 2ኛ ምዕራፍ ዕቅድና ትግበራ አቅጣጫዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ኅዳር 03/2015 ዓ.ም ውይይት አካሂዷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በ“RUNRES/ረንረስ” ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2ኛ ምዕራፍ ዕቅድና የትግበራ አቅጣጫ ላይ ውይይት ተካሄደ
- Details
ትምህርት ሚኒስቴር የ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና አሰጣጥ ሂደት ስኬታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅዖ ላበረከቱ የፀጥታ አካላት፣ የትምህርት ቢሮዎች፣ ዩኒቨርሲቲዎችና እና ሌሎች ተቋማት የምስጋናና የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሰጥቷል። ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ትምህርት ሚኒስቴር ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምስጋናና የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሰጠ
- Details
ቀጠናዊ የኢንዱስትሪ ትስስር ፎረሙ ከአከባቢው ኢንዱስትሪዎችና ቴክ/ሙ/ትም/ሥ/ኮሌጆች በዳሰሳ ጥናት የተገኙ ውጤቶች፣ የ2014 ዕቅድ አፈፃፀምና የ2015 ዓ.ም ዕቅድ ዙሪያ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ጥቅምት 26/2/2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ተወያይቷል፡፡ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ቀጠናዊ የእንዱስትሪ ትስስር ፎረም ጉባዔ በአርባ ምንጭ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ተካሄደ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ2014 ዓ/ም ምሩቃን በብቃት መመዘኛ ፈተና አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል፡፡ የብቃት መመዘኛ ፈተናው በፌዴራል ጤና ሚኒስቴርና በከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ በየዓመቱ የሚሰጥ ነው፡፡
Read more: የ2014 ዓ/ም በሕክምናና ጤና ሳይንስ ምሩቃን በብቃት መመዘኛ ፈተና አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በሒሳብ ትምህርት ከፍል በ‹‹Opበአርባ ምንጭ ዩኒቨርeration Research›› ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ዕጩ ዶ/ር ሀብታሙ ፀጋዬ የምርምር ሥራቸውን ኅዳር 3/2015 ዓ/ም የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርበው ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ