- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከ ̋UNHCR” ጋር በጋራ በመተባበር ከጋሞ፣ ጎፋ እና ኮንሶ ዞኖች፣ እንዲሁም ደራሼ እና አሌ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንቶችና ም/ፕሬዝደንቶች፣ ዳኞች፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች ፣ አቃቢያን ሕጎች፣ የነጻ ሕግ ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ጋር በነፃ የሕግ ድጋፍና በካምፓላ ስምምነት ዙሪያ ኅዳር 1/2015 ዓ/ም የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በነፃ የሕግ ድጋፍና በካምፓላ ስምምነት ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ
- Details
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር 16ኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ወርን ‹‹ትምህርትና የወጣቶች ስብዕና ግንባታ›› በሚል ርዕስ ኅዳር 1/2015 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው አክብረዋል፡፡ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝደንት እና በምክትል ኘሬዝደንት ማዕረግ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ውድድር የቀረቡ ተወዳዳሪዎች የስትራቴጅክ ዕቅድ ገለፃ የሚያቀርቡት፤
- ለኘሬዝደንትነት የሚወዳደሩ በ05/03/2015 ዓ.ም እና
- ለውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተርነት የሚወዳደሩ በ06/03/2015 ዓ.ም
- Details
ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝደንት ለመምረጥ በ19/12/2014 ዓ.ም በወጣው የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ መሠረት ከተመዘገቡ ተወዳዳሪዎች ዝቅተኛውን መስፈርት በማሟላት የቀረቡ ተወዳዳሪዎች በመመሪያው መሠረት የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት እና ነባር መምህራን ወይም ተመራማሪዎች በተገኙበት የስትራቴጅክ ዕቅድ ገለጻ የሚደረግ ስለሆነ የኢንስቲትዩቶች፣ የኮሌጆች እና የት/ቤቶች ዲኖችና ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች እንዲሁም የአስተዳደር ዳይሬክተሮች ከየዘርፋችሁ የካውንስል አባላት እና ከየትምህርት ክፍሉ አንድ አንድ ነባር/Senior/ መምህር ወይም ተመራማሪ ይዛችሁ በ5/03/2015 ዓ.ም 2፡3ዐ በዋናው ግቢ መግቢያ በር አካባቢ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝደንትነት ውድድር የስትራቴጅክ ዕቅድ ገለፃ ተሳታፊዎች ጥሪ ማስታወቂያ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት አማካኝነት በምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርገው የተዘጋጁ 35 ንድፈ-ሃሳቦች ቀርበው ከጥቅምት 24-25/2015 ዓ/ም ግምገማ ተካሂዶባቸዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የምርምርና የማኅበረሰብ ጉድኝት ንድፈ-ሃሳቦች ተገመገሙሙ