አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በዓይነቱ ልዩ የሆነ ነጻ የዓይን ምርመራና የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ሕክምና (Cataract Surgery) አገልግሎት ከአሜሪካ በሚመጡ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው የዓይን ስፔሻሊስት ሐኪሞች ጋር በመተባበር ከመጋቢት 25 - 30/2015 ዓ/ም ድረስ በሆስፒታሉ ይሰጣል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ለአዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች ከመጋቢት 01-02/2015 ዓ/ም የሕይወት ክሂሎት/Life Skill/ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ለ2015 ዓ/ም አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች የካቲት 30/2015 ዓ/ም የእንኳን ደኅና መጣችሁ መርሃ ግብር አዘጋጅተዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ማዕከል ማስ/ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማው ከሚገኙ ሆስፒታልና ጤና ጣቢያዎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በወባ በሽታ ምርመራ፣  ሕክምና አሰጣጥ፣ ቁጥጥርና መከላከል አዳዲስ አሠራሮች ዙሪያ ከመጋቢት 1-3/2015 ዓ/ም ድረስ የቆየ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡