Arba Minch University (AMU) is implementing Swiss Agency for Development and Cooperation (SDC) funded research and development project called RUNRES: The Rural - Urban Nexus: Establishing a nutrient loop to improve city region food system resilience in collaboration with ETH Zurich, Switzerland, IITA in DRC and Rwanda and University of KwaZulu Natal in South Africa. Following successful completion of Phase I, the project's second phase (2023 – 2027) will start operations in October 2023 and focus on scaling innovations piloted in the previous phase. During the first phase, the project team found that most small and medium enterprises (SME) selected to test innovations lack a proper understanding and capacity to develop and implement business plans. As we transitioning into the second phase, focusing on scaling, it is crucial to provide business development service (BDS) to enterprises. As a result, we are planning to hire independent part-time business expert for the project.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖቶች ተከታይ ለሆነው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብና የቀድሞ ምሩቃን እንዲሁም ለመላው የእምነቶቹ ተከታዮች እንኳን ለነብዩ መሐመድ 1,498 የልደት በዓል እና ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ እያለ በዓላቱ የሠላም፣ የጤና እና የደስታ እንዲሆኑላችሁ ከወዲሁ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሳውላና ጂንካ ከተሞች በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር በኅብረሰተሰብ ጤና ትምህርት የ2 ዲግሪያቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች የልማታዊ የቡድን ሥልጠና ፕሮግራምን/Developmental Team Training Program /DTTP/ መሠረት በማድረግ በሳውላ ዶዛ ቀበሌ የላ ቀጠና እንዲሁም በጂንካ ብሩህ ተስፋ ንዑስ ቀበሌ በኮይዳ ቁጥር ሁለት መንደር የአካባቢውን ማኅበረሰብ በማስተባበር ከሰባት መቶ ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነቧቸው የጋራ መጸዳጃና ሻወር ቤት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መስከረም 13 እና 14/2016 ዓ/ም በይፋ ተመርቀው ለማኅበረሰቡ ተላልፈዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ከአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት እና ከጋሞ ልማት ማኅበር ጋር በመተባበር ከከተማው ወጣት አደረጃጀት ለተወጣጡ ወጣቶች በሕይወትና የአእምሮ ውቅር    ዙሪያ ከመስከረም 8-11/2016 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ያሠለጠናቸውን 91 ወንድና 58 ሴት በድምሩ 149 የ6 ባች ተማሪዎች ለ2 ዙር  መስከረም 13/2016 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡