- Details
Arba Minch University (AMU) is implementing Swiss Agency for Development and Cooperation (SDC) funded research and development project called RUNRES: The Rural - Urban Nexus: Establishing a nutrient loop to improve city region food system resilience in collaboration with ETH Zurich, Switzerland, IITA in DRC and Rwanda and University of KwaZulu Natal in South Africa. Following successful completion of Phase I, the project's second phase (2023 – 2027) will start operations in October 2023 and focus on scaling innovations piloted in the previous phase. During the first phase, the project team found that most small and medium enterprises (SME) selected to test innovations lack a proper understanding and capacity to develop and implement business plans. As we transitioning into the second phase, focusing on scaling, it is crucial to provide business development service (BDS) to enterprises. As a result, we are planning to hire independent part-time business expert for the project.
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖቶች ተከታይ ለሆነው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብና የቀድሞ ምሩቃን እንዲሁም ለመላው የእምነቶቹ ተከታዮች እንኳን ለነብዩ መሐመድ 1,498ኛ የልደት በዓል እና ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ እያለ በዓላቱ የሠላም፣ የጤና እና የደስታ እንዲሆኑላችሁ ከወዲሁ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሳውላና ጂንካ ከተሞች በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር በኅብረሰተሰብ ጤና ትምህርት የ2ኛ ዲግሪያቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች የልማታዊ የቡድን ሥልጠና ፕሮግራምን/Developmental Team Training Program /DTTP/ መሠረት በማድረግ በሳውላ ዶዛ ቀበሌ የላ ቀጠና እንዲሁም በጂንካ ብሩህ ተስፋ ንዑስ ቀበሌ በኮይዳ ቁጥር ሁለት መንደር የአካባቢውን ማኅበረሰብ በማስተባበር ከሰባት መቶ ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነቧቸው የጋራ መጸዳጃና ሻወር ቤት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መስከረም 13 እና 14/2016 ዓ/ም በይፋ ተመርቀው ለማኅበረሰቡ ተላልፈዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ከሰባቶ መቶ ሺህ ብር በላይ በሆነ ወጪ በሳውላና ጂንካ ከተሞች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የጋራ መጸዳጃና ሻወር ቤት ፕሮጀክቶች ተመረቁ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ከአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት እና ከጋሞ ልማት ማኅበር ጋር በመተባበር ከከተማው ወጣት አደረጃጀት ለተወጣጡ ወጣቶች በሕይወትና የአእምሮ ውቅር ዙሪያ ከመስከረም 8-11/2016 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ከአርባ ምንጭ ከተማ ለተወጣጡ ወጣቶች በሕይወትና የአእምሮ ውቅር ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ያሠለጠናቸውን 91 ወንድና 58 ሴት በድምሩ 149 የ6ኛ ባች ተማሪዎች ለ2ኛ ዙር መስከረም 13/2016 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ያሠለጠናቸውን 6ኛ ባች ተማሪዎች ለ2ኛ ዙር አስመረቀ