- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2014 የትምህርት ዘመን በመደበኛ፣ በማታ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ-ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከዚህ በታች በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች ተቀብሎ ማሠልጠን ይፈልጋል፡፡
- Details
በጫሞ ሐይቅ ዙሪያ ለሚሠራው አሳታፊ ዘላቂ የመሬትና የውሃ አያያዝ ሥራ ዕቅድ አዘገጃጀት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ከ10 ወረዳዎች ለተወጣጡ 58 የልማት ጣቢያ ሠራተኞችና የዘርፉ ባለሙያዎች ከሐምሌ 13/2012 ዓ/ም ጀምሮ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዓባያ ካምፓስ ለ7 ቀናት ተሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በጀርመን ልማት ተራድኦ ድርጅት/GIZ/ እና በግብርና ሚኒስቴር የዘላቂ መሬት አያያዝ ፕሮጀክት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በአሳታፊ ዘላቂ የመሬትና የውሃ አያያዝ ሥራ ዕቅድ አዘገጃጀት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
በ1ኛ ዓመት የክረምት መርሃ-ግብር ለመመዝገብ አመልክታችሁ የስም ዝርዝራችሁ በማስታወቂያ ሠሌዳ የተገለፀ ተማሪዎች የትምህርት ክፍያና የምዝገባ ጊዜ ከነገ 29/11/2013 - 1/12/2013 ዓ.ም በመሆኑ በተከታታይና ርቀት ትምህርት ኮሌጅ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በመቅረብ የማስታወቂያ ሠሌዳው ላይ የተለጠፈውን የትምህርት ክፍያ ዝርዝር በማየት ክፍያ እየፈፀማችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተከታታይና ርቀት ት/ኮሌጅ
- Details
የ2013 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ምዝገባ የሚካሄደው ከሐምሌ 26-27/2013 ዓ.ም ሲሆን፡-
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ነባር የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች በሙሉ
- Details
የእንግሊዝ ኤምባሲ የ UK መንግሥት የ “Chevening Scholarship Award” አሰጣጥን በተመለከተ በ28/11/2013 ዓ/ም የመጀመሪያ ዲግሪ ላላቸው የአ/ም/ዩ መምህራንና ሠራተኞች በበይነ-መረብ ማብራሪያ ይሰጣል ፡፡
በመሆኑም የመጀመሪያ ዲግሪና ሁለት ዓመት የሥራ ልምድ ያላችሁ ሠራተኞች ለመወዳደር የሚያስችለውን ግንዛቤ ለማግኘት ከላይ በተጠቀሰው ዕለት ከቀኑ 8፡00 - 9፡30 ድረስ የሚካሄደውን ውይይት ከታች በቀረበው አድራሻ በመጠቀም መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡