- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የብዝሃ-ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማዕከልና የእንሰትና የመድኃኒት ዕፅዋት ምርምርና ጥበቃ ፓርክ የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የምርምር ሥራዎችን እየከናወነ ነው፡፡
የብዝሃ-ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማዕከል ዳይሬክተርና የሆርቲካልቸር ት/ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ሰይፉ ፈቴና የምርምር ማዕከሉ በዋናነት የዘር ምንጭ ሆኖ ለምርምርና ለማስተማሪያነት እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የእንሰት ዝሪያዎችን በመንከባከብና በመጠበቅ እንዲሁም በእንሰት ዝሪያዎች ላይ የሚከሰቱ አንዳንድ ችግሮችን በሳይንሳዊ መንገድ ጥናትና ምርምር በማካሄድ በመለየት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየተሠራ ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የብዝሃ-ሕይወት፣ የእንሰትና የመድኃኒት ዕፅዋት ምርምርና ጥበቃ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለፀ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በ<<Public Health Nutrition>> እና በ<<Clinical Bio-Chemistry>> የ2ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመክፈት የሚያስችል የውጭ ሥርዓተ-ትምህርት ግምገማ መስከረም 7/2013 ዓ/ም አካሂዷል፡፡
የአካዳሚክ ጉ/ም/ፕሬዝደንት ተወካይ ዶ/ር ንጉሴ ታደገ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ እንደ ሀገር ከተለዩ 8 የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች መካከል መሆኑን አስታውሰው መሰል የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች መከፈታቸው ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ተልዕኮ እንዲወጣ ከማድረግ አንፃር ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የሚከፈቱ አዳዲስና ነባር የትምህርት ፕሮግራሞችን ጥራት ለማረጋገጥም በትኩረት ይሠራል ብለዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2013 የት/ዘመን በህክምናና ጤናው ዘርፍ ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ፕሮግራሞችን ሊከፍት ነው
- Details
The whole world is going through the toughest times of the century. The pandemic has brought the entire world upside down. No one claims itself to be indisposed; the pandemic has affected each and every person’s life in one or the other way irrespective of caste, creed, race, geographic boundaries, or economic status. The coronavirus has infected 27 million people and the death toll is reaching near to 1 million, with such an exponential growth rate every day is coming with a greater challenge.
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የባዮሎጂ ትምህርት ክፍል በ‹‹Infectious Diseases›› 3ኛ ዲግሪ እንዲሁም በ ‹‹Bio-Medical Sciences›› 2ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመክፈት የሚያስችለውን የውጭ ሥርዓተ-ትምህርት ግምገማ ነሐሴ 26/2012 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የቤኒፊት ሪያላይዝ ፕሮግራም ክልላዊ የአማካሪ ምክር ቤት ጉባዔ በመስክ ጉብኝትና የ2020 የ6 ወራት ሪፖርት ግምገማ በማድረግ ከነሐሴ 26 - 27/2012 ዓ/ም ለሁለት ቀናት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የሐዋሳና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሮጀክት አፈፃፀም ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ