- Details
ውድና የተከበራችሁ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተገባዶ የመጀመሪያዉ ደረጃ የዉሃ ሙሌት በመጠናቀቁ በድጋሚ እንኳን ደስ አለን፡፡ ቀሪዉን የግንባታ ሥራ ለማጠናቀቅ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፍተኛ ተነሳሽነት በማሳየት ላይ ይገኛል፡፡ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማገኅበረሰብም ቀደም ሲል ስናደርግ እንደነበርነዉ ሁሉ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይም የዜግነት አሻራችንን ማስቀመጡን መቀጠል ይጠበቅብናል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
- Details
The Foundation Fiat Panis in its 12th August, 2020, press release issued at Ulm, Germany, stated that its biennial Josef G Knoll European Science Award 2020 is awarded to 3 praiseworthy researchers, AMU’s researcher and lecturer, Dr Addisu Fekadu, who did PhD from KU Keuven, Belgium; followed by Zambian Dr Thomas Daum, University of Hohenheim and Dr Arndt Feuerbacher of Humboldt University of Berlin.
Read more: Dr Addisu Fekadu wins Josef G Knoll European Science Award 2020
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት አባላትና አመራሮች በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ካምፓሶች እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ሥራዎች ያሉበትን ሁኔታ ሐምሌ 10/2012 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ልማት ም/ፕሬዝደንት ወ/ሮ ታሪኳ ወ/መድኅን ጉብኝቱ በዩኒቨርሲቲ በካፒታል በጀት እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ የግንባታ ፕሮጀክቶች ያሉበትን የአፈፃፀም ደረጃና ተግዳሮቶች በአካል በማየት ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫና ውሳኔ ለመስጠት የሚረዱ ሀሳቦች ለማግኘት የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ መሰል ጉብኝቶች ለዘርፉ ያላቸው ፋይዳ ጉልህ መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ ታሪኳ በዩኒቨርሲቲው ተጀምረው የቆዩ በዋናው ግቢና ዓባያ ካምፓስ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ከኮንትራክተሮቹ ጋር የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን እንዲሁም ሌሎች ስትራቴጂዎች ተቀይሰው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና ሕክምና የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሐምሌ 9/2012 ዓ/ም ድጋፍ አድርጓል፡፡
በዕለቱ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በሆስፒታሉ ተገኝተው የተቋሙን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይ ዩኒቨርሲቲውና ሆስፒታሉ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመሥራት ከስምምነት ደርሰዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለኮሮናቫይረስ ለመከላከልና ሕክምና የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አበረከተ