- Details
በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሀገር በቀል 3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በ“Irrigation Engineering”፣ “Ground Water Engineering”፣ “Water Supply and Sanitary Engineering” ለመማር ያመለከታችሁ አመልካቾች እና የመጀመሪያውን ምልመላ ያለፋችሁ አመልካቾች የ“Home-Grown Collaborative PhD Programs (HCPP)” ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ ባለመኖሩ በዩኒቨርሲቲው መደበኛ የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም መቀጠል የምትፈልጉ የመጨረሻውን የመግቢያ ፈተና በቀን 30/3/2014 ዓ.ም የሚሰጥ ስለሆነ ፍላጎቱ ያላችሁ ከላይ በተጠቀሰው ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ በአካል በመገኘት እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት 10 ሚሊየን ብር እንዲሁም በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን ከተማ ለተጠለሉ ወገኖች የሚውል አንድ ሚሊየን ብር የሚያወጣ የምግብ እህል ድጋፍ ኅዳር 14/2014 ዓ/ም አድርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለሀገር መከላከያ ሠራዊትና ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

- Details
የዩኒቨርሲቲው “RUNRES” ፕሮጀክት ከመጀመሪያ ዙር ቆይታው የ2 ዓመታት አፈፃፀሙን ለመቃኘት ኅዳር 02/2014 ዓ/ም በኃይሌ ሪዞርት ወርክሾፕ አዘጋጅቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ “RUNRES” ፕሮጀክት የአፈፃፀም ቅኝት ወርክሾፕ አካሄደ
- Details
ከአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች በኢንተርንሺፕ ላይ የቆያችሁ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መመለሻ ጊዜ ኅዳር 24/2014 ዓ.ም ሲሆን የመመዝገቢያ ጊዜ ከኅዳር 24-26/2014 ዓ.ም መሆኑን እያሳወቀ ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመለሱ በኢንተርንሺፕ ላያ የቆያችሁበትን ሪፖርት አጠናቅቃችሁ ለሚመለከተው ፋከልቲ ገቢ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው በጥብቅ ያሳስባል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ከአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ለባለድርሻ አካላት፣ ለቢሮ ኃላፊዎችና ከ19ኙ ቀበሌያት ለተወጣጡ 70 በጎ መልዕክተኞች ከኅዳር 2-4/2014 ዓ/ም በአስተሳሰብ ለውጥና በማኅበራዊ ጉዳይ ተግባራት ላይ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ባለድርሻ አካላትና ለበጎ መልዕክተኞች የስብዕና ግንባታ ሥልጠና ሰጠ