- Details
ባሉበት
ውድ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ፣ ለመላዉ ዓለምም ሆነ ለሀገራችን ሰው ልጅ ሁሉ በሕይወት ለመኖር እጅግ ከፍተኛ ስጋት ያመጣዉ የኮቭድ-19 መከሰት ምክንያት ለሕዝብና ለሀገር ደህንነት ታስቦ በትኩረት እየተሠራ ካለዉ አንጻር በሀገራችን የሁሉም ትምህርት ደረጃ ተማሪዎች ወላጅ ወይም ቤተሰብ ዘንድ እንዲቆዩ በተደረገዉ ሂደት ከመጋቢት 19 እስከ 21/2012 ባሉት ቀናት ከዩኒቨርሲቲዉ ግቢ ወጥታችሁ ወደየቤተሰቦቻችሁ ዘንድ ከሄዳችሁበት ቀን ጀምሮ እንደምን አላችሁ? ውድ ተማሪዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 6ቱም ግቢዎች የሚሞቁትና የሚያምሩት እናንተ ስትኖሩበትና በግቢያችሁ ወዲያ ወዲህ (ከዶርም ወደ ክፍል፣ ከክፍል፣ ወደ ላይብራሪና ማጥኛ ቦታዎች፣ ወደ ሻይ/ቡና ወይም መዝናኛ ቦታዎች፣ ወደ አቢያተክርስቲያናትና መስጂዶች ከዚያም ወደ ግቢ፣ ወደ ከተማና ከዚያም ወደ ግቢያችሁ) ሽርጉድ እያላችሁ ስትመላለሱ ብቻ ነዉ፡፡ በክረምት ዕረፍት ለሁለት ወራት ወደ ቤተሰብ ስትሄዱ የክረምት ተማሪዎች ይተኩ ነበር፡፡ አሁን ግን ማንም ተማሪ የለም፡፡ የትምህርት ቤት/ተቋም ትልቁ የውበት ምንጭና ሕይወት ተማሪ ነዉ፡፡
Read more: ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት የተላለፈ መልዕክት ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ
- Details
In order to complement the ongoing global efforts to study and understand the catastrophic implications of COVID-19, Arba Minch University acting on the directive of Ministry of Science and Higher Education has constituted a Research Council that will soon launch specific research projects to study broader aspects that were left totally upended in the wake of Corona virus outbreak in recent times.
Read more: Special Research Council to conduct COVID-19 related research
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና በሽታን ስጋት ተከትሎ በአርባ ምንጭ ከተማ ለተቋቋመው ለይቶ ማቆያ ማዕከል የአልጋ፣ የፍራሽና የአንሶላ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በተለምዶ ኩልፎ ካምፓስ ተብሎ በሚታወቀው የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኙ የተማሪ ማደሪያዎችንም ለለይቶ ማቆያ ለማዋል የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ እንዳሉት የኮሮና በሽታን ለመከላከልና አስከፊ ጉዳት እንዳያደርስ በሚደረገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው የበኩሉን ሚና እንደሚወጣና እየተወጣም መሆኑን ገልፀው ለለይቶ ማቆያው የተደረገው ድጋፍም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአርባ ምንጭ ከተማ ቡቡ ሜዳ ለተቋቋመው ለይቶ ማቆያ ማዕከል የቁሳቀስ ድጋፍ አደረገ
- Details
AMU in association with Gamo Zone administration has jointly constituted Corona Task Force to prevent possible transmission of virus in the community. CTF has 40-member main committee with nine sub-committees to launch awareness campaign at zonal level, ensure sample testing; establish quarantine facilities to prevent further spread of virus and treatment aspect as well.
Gamo Zone Administrator, Mr Berhanu Zewde, heading CTF, said, all the committees will look into aspect such as communication, water sanitation, security, transport, etc. Zonal authority will contribute ETB 3 million and mobilize more resources in kind and cash from people across society, governmental and non-governmental organizations to support this social endeavor to tackle this catastrophe.Click here to see the pictures
Read more: AMU, Gamo Zone form Corona Task Force to contain transmission
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተቋቋመው ግብረ-ኃይል ንዑስ ግብረ-ኃይል አባል የሆኑ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጤና ባለሙያዎች በአርባ ምንጭ ከተማ እንዲሁም በአርባ ምንጭ ዙሪያ፣ ጨንቻ፣ ካምባ፣ ገረሴና ቆጎታ ወረዳዎች በመገኘት በኮሮና ቫይረስ መከላከያ፣ መተላለፊያና ሊደረጉ በሚገባቸው ጥንቃቄዎች ዙሪያ ለአካባባቢው ማኅበረሰብ፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ አከናውነዋል፡፡
ግብረ-ኃይሉ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ እና በክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺይፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ታምሩ ሽብሩ አማካኝነት በሲቀላ ገበያ በኮሮና ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ መጋቢት 25/2012 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት እንዲተላለፍ አድርጓል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ