• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024
photo_2024-02-21_10-01-18.jpeg
photo_2025-05-06_09-54-21.jpeg
photo_2025-05-06_09-54-38.jpeg
1.jpeg
2.jpeg
previous arrow
next arrow

የሐዘን መግለጫ

Details
Tue, 27 June 2023 8:14 am

ወ/ሮ ትዕግስት አበራ ከአባታቸው አቶ አበራ ከበደ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ምሳኤ ምትኩ በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ሚያዝያ 03/1970 ዓ/ም ተወለዱ፡፡ የ1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ ከተማ ኃይሌ ደጋጋ 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃና መሠናዶ ት/ቤት ተከታትለዋል፡፡

Read more: የሐዘን መግለጫ

የሐዘን መግለጫ

Details
Tue, 27 June 2023 7:38 am

አቶ ማቴዎስ ገነሞ ከአባታቸው ከአቶ ገነሞ ዶክሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ማታፌ ጩቃሎ በቀድሞ በወላይታ ክፍለ ሀገር በአረካ ወረዳ አርፍጣ አጅማንቾ ቀበሌ ጥር 1/ 1956 ዓ/ም ተወለዱ፡፡

Read more: የሐዘን መግለጫ

ለአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራንና ተመራማሪዎች በዲጂታል ፕሮግራሚንግ፣ ሞዴሊንግ እና የመረጃ አጠቃቀም ላይ ሥልጠና ተሰጠ

Details
Tue, 27 June 2023 7:24 am

ለአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራንና ተመራማሪዎች በዲጂታል ፕሮግራሚንግ፣ ሞዴሊንግ እና የመረጃ አጠቃቀም ዙሪያ ከሰኔ 3 - 5/2015 ዓ/ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Read more: ለአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራንና ተመራማሪዎች በዲጂታል ፕሮግራሚንግ፣ ሞዴሊንግ እና የመረጃ አጠቃቀም ላይ ሥልጠና ተሰጠ

የተግባር ተኮር ልምድ ልውውጥ ያደረጉ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህራን የቆይታ ሪፖርት አቀረቡ

Details
Tue, 27 June 2023 7:12 am

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ የሥራ ፈጠራ ኢንስቲትዩት፣ ከሲሳይ ፕሮሞሽን ኢቨንት አዘጋጅ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዝየም እና ከጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል ጋር ያደረጉትን የተግባር ተኮር ልምድ ልውውጥ ሪፖርት ሰኔ 3/2015 ዓ/ም አቅርበዋል፡፡ በዕለቱም በዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ አጋርነት ትስስር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡  ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የተደረገው የተግባር ተኮር ልምድ ልውውጥም ‹‹Assessment of Entrepreneurship and Business Development Practices of Entrepreneurship Development Institute (EDI)››፣ ‹‹Exchanging Knowledge in the Pre, on and Post Event Phases & Networking with Industry in Sisay Aderisse Promotion & Event Organizer Cooperative››፣ ‹‹Establishing Strategic Partnership and Experience Sharing with Hospitality Organization: Training Exposure at Jupiter International Hotel›› እና “Practices, Challenges and Gaps Between Theory and Practice in Museum Management: An Externship on the National Museum of Ethiopia›› ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት እና የፕሬዝደንት ተወካይ ዶ/ር ዓለማየሁ ጩፋሞ እንደገለጹት የኢንደስትሪ ትስስር መፈጠሩ ወደ ማኅበረሰቡ መውረድ የሚችሉ ምርምሮችን ለመሥራት እና ተግባር ተኮር ትምህርት በመስጠት ገበያው የሚፈልገውን ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ ም/ፕሬዝደንቱ አክለውም ትምህርት በየወቅቱ ራስን ማብቃት የሚፈልግ በመሆኑ በቀጣይ ተቋሙ ለሚያመራው  የራስ ገዝ ጉዞ ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ ያሉ የተቋሙ ሠራተኞች የሥራ ፈጠራ ልምድ እንዲያካብቱ የተሻለ የተግባር ተሞክሮ ባላቸው መምህራን ታቅዶ ሊሠራበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ኮሌጁም በዚህ ረገድ እያካሄደ ያለው ተግባር የሚበረታታ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡

የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ  ዲን ዶ/ር መስፍን መንዛ በበኩላቸው መርሃ ግብሩ ለሁለተኛ ጊዜ መከናወኑን አስታውሰው  በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካካል ያለው ግንኙነት የጠበቀ ባለመሆኑ ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ አመላክተዋል፡፡ በመሆኑም የሁለቱ ወገን ስምምነት ዋና ዓላማ  ያላቸውንና በቀጣይ የሚኖራቸውን የሰው ኃይል አሠራር፣ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር በማድረግ የተግባር ልምድና በጀት በማስተባበር የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት ውጤታማ በሆነ መልኩ በጋራ ለመወጣት የሚያስችል የማስፈጸም አቅም መፍጠር  እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም በጥናትና ምርምር ላይ በመመርኮዝ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ ብሎም ሀገሪቷን ተወዳዳሪ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ዲኑ ገልጸዋል፡፡

የሥራ ላይ ልምድ ልውውጥ ሪፖርት ያቀረቡ መምህራን በንድፈ ሃሳብ የሚያስተምሩትን ትምህርት በተግባር መመልከትና  የራሳቸውን የክሂሎት ክፍተት መሙላት የቻሉበት፣ በመምህራኑ ተለይተው በቀረቡ የኢንደስትሪው ተጨባጭ ችግሮች ዙሪያ  በቀጣይ የጋራ የሆነ ጥናት በማካሄድ ችግሮች እንዲፈቱ እንዲሁም ለሥርዓተ-ትምህርት ክለሳ ገንቢ የሆነ አስተያየት የተሰበሰበበትና ፍሬያማ ውይይት የተደረገበት እንደነበር ዶ/ር መስፍን ተናግረዋል፡፡   

የኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖለጂ ሽግግር ሥራ ከተቋሙ ተልዕኮ አንዱ ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ቶሌራ ሴዳ ዩኒቨርሲቲውን ከሌሎች ተቋማት ጋር በማስተሳሰር በቴክኖሎጂ የሚፈጠሩ ሃሳቦችን ወደ እንደስትሪው እንዲሄዱ  የማድረግ ሥራ እንደሚሠራ ገልጸው የተግባር ልምዳቸውን ያቀረቡት መምህራን በንድፈ ሃሳብ ያላቸውን ዕውቀት በተግባር የማስደገፍ ሥራ እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ቶሌራ አክለውም በቀጣይ የኢንደስትሪ ችግሮች ላይ በጋራ ምርምሮችን በመሥራት የኢንደስትሪውን ችግር በዘላቂነት መፍታትና እንደ ሀገር ሁሉም ተቋማትና ማኅበረሰብ በጋራ በመሥራት ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ የተፈራረሙ አካላትም በቀጣይ በሚኖሩ መርሃ ግብሮች አባል በመሆን እንዲሳተፉና በውል ስምምነቱ መሠረትም ወደ ሥራ እንዲገቡ አሳስበዋል፡፡

የሥልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የቀረቡ ሪፖርቶች የኢንደስትሪ ተቋማትን ጥንካሬና ድክመቶችን ያመላከተና መምህራኑ የተግባር ሥራዎችን በተገቢው የተማሩበት በመሆኑ የሚበረታታ ነው፡፡ የትብብር ሥራዎች ተጠናክረው በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ተሞክሮዎች ተቀምረው መምህራን ልምድ እንዲያካብቱ፣ የትምህርት ሥርዓቱ እንዲሻሻል ማድረግና ተግባር ተኮር እንዲሆን መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡ በቀጣይ በሚኖሩ የጋራ የሥራ ተግባራት ጠንክረው በመሥራት የተሻሉ ተማሪዎችን ለማፍራትና  የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በፕሮግራሙ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት፣ የዩኒቨርሲቲው ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፣ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን፣ የኢትዮጵያ የሥራ ፈጠራ ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ የሲሳይ ፕሮሞሽን ኢቨንት አዘጋጅ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ሥራ አስኪያጅ፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሙዝየም ዳይሬክተር፣ በኢትዮጵያ ኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኪሊንቶ ኢንደስትሪያል ፓርክ ሲኒየር ኢንቫይሮሜንታሊስት ባለሙያ፣ የኮሌጁ መምህራንና ሌሎች  ተጋባዥ ባለድርሻ አካላት ታድመዋል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCCD/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሴት መምህራን ፎረም ተቋቋመ

Details
Tue, 27 June 2023 6:54 am

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጃፓይጎ ‹‹Jhpiego›› ከተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር የሴት መምህራን ፎረም/Women Academic Forum/ ለመመሥረት ሰኔ 02/2015 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Read more: በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሴት መምህራን ፎረም ተቋቋመ

  1. የዕጩ ዶ/ር መሳይ ሳሙኤል የ3ኛ ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፍ ተገመገመ
  2. 21ኛው ዓለም አቀፍ ዘላቂ የውኃ ሀብት ልማት ሲምፖዚየም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ
  3. AWTi hosts the 21st Global Meet on Sustainable Water Resources Development
  4. 50ኛው የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን ተከበረ

Page 153 of 513

  • 148
  • 149
  • 150
  • 151
  • 152
  • 153
  • 154
  • 155
  • 156
  • 157

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2024 Arba Minch University. Built by Meftihe.

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap