- Details
“TAY Authorized Accountants and Auditors” የተሰኘ ድርጅት ነጸ የ3 ወራት የኢንተርንሺፕ ፕሮግራም ያዘጋጀ ስለሆነ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስ እና አካውንቲንግና ፋይናንስ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቃችሁ ምሩቃን ከዚህ ቀጥሎ ባለው ማስፈንጠሪያ መመዝገብ የሚትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ማስፈንጠሪያው - https://www.tayauditing.com/internship-programs/
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
- Details
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስከ አሁን ባለው አፈጻጸም የሦስቱም ዙሮች የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቆ 2ኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተሰማውን ከፍተኛ ደስታ ለመግለጽ ይወዳል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ፣ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የምትኖሩ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ምሩቃን እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ባለ ድልና ባለ ዕድል ትውልድ ለመሆን አበቃን፡፡
Read more: በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛ ተርባይን ሥራ መጀመር ምክንያት የተሰጠ የደስታ መግለጫ
- Details
የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከደቡብ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲና ከደቡብ ክልል ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ጋር በመተባበር በመሎ ኮዛ ወረዳ ጨልቆ ወንዝና በቡርጂ ወረዳ ሰገን ወንዝ ላይ ለሚያሠራቸው የግድብና መስኖ ፕሮጀክቶች የጥናትና ዲዛይን ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ነሐሴ 2/2014 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች አቅርቧል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2015 የትምህርት ዘመን በመደበኛ፣ በማታ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብሮ መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከዚህ በታች በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች ተቀብሎ ማሠልጠን ይፈልጋል፡፡ የፕሮግራሞችን ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በ 2015 የትምህርት ዘመን በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ለመማር የምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና በመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ትብብር በግንባታ፣ በምክር አገልግሎት ግዥ፣ በውል አስተዳደርና ንብረት አያያዝ ዙሪያ ከነሐሴ 4-7/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናና የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡
የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ወልደአብ ደምሴ የሥልጠናው ዓላማ የተሻሉ ተሞክሮዎችን በማጋራትና ግንዛቤ በማስጨበጥ የግዥ አሠራሮች እንዲሻሻሉ እንዲሁም ባለሙያዎቹ የአመለካከት ለውጥ አምጥተው የራሳቸውን አሻራ ማሳረፍ እንዲችሉ ማስቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የግዥ ሥራ ጊዜ የማይሰጥና ውስብስብ በመሆኑ የሚሻሻሉ አዋጆችና የመመሪያ ለውጦችን በማየት ፈጻሚዎች በመተባበር እና ሕግና ሥርዓቱን ተከትሎ በመሥራት ኃላፊነታቸውን መወጣትና ራሳቸውን ማሻሻል እንደሚገባቸው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በግንባታ፣ በምክር አገልግሎት ግዥ፣ በውል አስተዳደርና ንብረት አያያዝ ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ