 
        
        - Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹STEM›› ማስተባበሪያ ማዕከል ከጋሞ፣ ጎፋ፣ ኮንሶ፣ ባስኬቶ፣ ጋርዱላ፣ አማሮ፣ አሌ እና ኮሬ ዞኖች ተወጣጥው ከሐምሌ 13/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለ45 ቀናት ሥልጠና ሲወስዱ የቆዩ 170 ተማሪዎች የሽኝት መርሐ ግብር ነሐሴ 30/2017 ዓ/ም አካሂዷል ፡፡ ሠልጣኝ ተማሪዎቹ ከ7ኛ- 11ኛ ክፍል የተወጣጡና በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት እንዲሁም የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ናቸው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በ2017 ዓ/ም የክረምት ‹‹STEM›› ሠልጣኝ ተማሪዎች የሽኝት መርሃ ግብር ተካሄደ
 
        
        - Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መረጃ እና መገናኛ ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት በሥሩ ለሚገኙ ከሁሉም ካምፓሶች ለተወጣጡ አዲስ ባለሙያዎች ከነሐሴ 19/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት የቆየ የቢሮ ማሽኖች እና ሌሎች ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ጥገና ላይ ያተኮረ የአቅም ማሻሻያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የቢሮ ማሽኖች እና ሌሎች ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ጥገና ላይ ያተኮረ የአቅም ማሻሻያ ሥልጠና ተሰጠ
 
        
        - Details
Arba Minch University (AMU) hosted a significant three-day event of staff introduction and RUNRES project phase II progress update on September 1st-3rd, 2025 to formally introduce its project team members to development partners from the Swiss Embassy and the Swiss Agency for Development and Cooperation (SDC). Click here to see more photos.
Read more: AMU-RUNRES Project Hosts Staff Introduction and Phase II Progress Update Event
 
        
        - Details
ዶ/ር ስምዖን ሽብሩ ከአባታቸው አቶ ሽብሩ ጨጨ እና ከእናታቸው ወ/ሮ አምኔ ጎሌ በቀደሞው ጋሞ አውራጃ በኦቾሎ ቀበሌ ግንቦት 29/1960 ዓ/ም ተወለዱ፡፡ ዶ/ር ስምዖን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በላንቴ 1ኛ ደረጃና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትለዋል፡፡ ዶ/ር ስምዖን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በባዮሎጂ የትምህርት መስክ ሐምሌ 3/1984 ዓ/ም፣ የማስተርስ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ሐምሌ 2/1991 ዓ/ም እንዲሁም የ3ኛ ዲግሪያቸውን ቤልጂየም ሀገር ከሚገኘው አንተወርፕ ዩኒቨርሲቲ እ.አ.አ የካቲት 25/2016 በ ‹‹Terrestrial Ecology›› የትምህርት ዘርፍ አግኝተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡






