አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በራስ ገዝ (Autonomous) አስተዳደር ራሱን ለማስተዳደር እያከናወነ ባለው እንቅስቃሴና ተቋሙ በሚገኝበት አሁናዊ ደረጃ ዙሪያ ከፍተኛ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች በተገኙበት ከዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት ጋር መጋቢት 8/2015 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ::

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለጫሞ ካምፓስ አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበልና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የ3እና 4 ዓመት ሴት ተማሪዎች የማበረታቻ መርሃ ግብር መጋቢት 7/2015 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድ/ማስ/ጽ/ቤት በሸክላ ሥራና በእንጨት ለቀማ የሚተዳደሩ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ገቢ በማሳደግ አኗኗር ማሻሻል የሚያስችሉ ሁለት ግራንድ ፕሮጀክቶችን ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መጋቢት 8/2015 ዓ/ም በይፋ ሥራ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ምርምር ማእከል ሳሶ ብሮይለር ብሪድ/Saso Broiler Breed/ ዝርያ ያላቸው ሁለት ሺህ ጫጩቶችን በግዥ በማስመጣት ያስጀመረው የዶሮ እርባታ ጣቢያ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እና የማእከሉ ተመራማሪዎች በተገኙበት መጋቢት 7/2015 ዓ/ም ተጎብኝቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር በገጠር መሬት አዋጅና ይርጋ ዙሪያ በጋሞ ዞን፣ በዞኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ የፍርድ ቤት ፕሬዝደንቶችና ዳኞች መጋቢት 09/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶ ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡