
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ‹‹Institute of Primary Health Care›› ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር ከአራት ጤና ጣቢያዎች ለተወጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የወጣቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሥልጠና ከነሐሴ 12-16/2017 ዓ/ም ለ5 ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የወጣቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ያለመ ሥልጠና ለጤና ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሰጠ

- Details
የሰላም ሚኒስቴር፣ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘውን የጎንደር ቃልኪዳን ቤተሰብ ፕሮጀክት /የፋሲለደስ ስምምነት/የሚሰኘውን ውል በዩኒቨርሲቲው ለማስቀጠል ያለመ የቃልኪዳን ውል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከአዩዳ ኢን አክስዩን ከተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት እና ከስፓኒሽ ዴቨሎፕመንት ኤጀንሲ ጋር በመሆን የሞሪንጋ ተክል ላይ በጋራ የሚሰራ የትብብር ፕሮጀክት ለማስጀመር በምዕራብ አባያ ወረዳ ዶሼ ቀበሌ እና በወላይታ ዞን አባላ አባያ በተሰኙ በተመረጡ ስፍራዎች የምሪንጋ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዛሬ ነሐሴ 13/2017 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከአለም ዓቀፍ የደን ምርምር ማዕከል(CFOR) እና ከአግሮፎረስትሪ ጋር በመተባበር በደጋና ወይና ደጋ የአየር ጸባይ የሚለሙ ከውጭ ሃገር የመጡ ተባይና በሽታን መቋቋም የሚችሉ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የተለያየ የግራርና የባህር ዛፍ ዝርያ ያላቸው ችግኞችን በማባዛት ለምርምርና የዘር ምንጭ ለማድረግ በግርጫ የምርምር ማዕከልና በኦቾሎ ኦዶ ቀበሌ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ነሃሴ 14 2017 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ተባይና በሽታን መቋቋም የሚችሉና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የተለያዩ የግራርና የባህር ዛፍ ዝርያዎች ችግኝ ተከላ ተካሄደ