የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ባች 1ኛ ዓመት ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች፣ የ2014 ባች 2ኛ ዓመት ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች እና የ2012 ባች 4ኛ ዓመት የህግ ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ቅበላ፣ ምዝገባ እና ትምህርት የሚጀመርበት ቀን እንደሚከተለው እንዲሆን ተወስኗል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን በድኅረ ምረቃ በሦስተኛ ዲግሪ ሦስት፣ በሁለተኛ  ዲግሪ 121 እና በቅድመ ምረቃ 1,348 እንዲሁም በፒጂዲቲ ሦስት በአጠቃላይ 1,475 የ36 ባች ተማሪዎችን ለሁለተኛ ዙር መስከረም 12/2016 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 395ቱ ሴቶች ናቸው፡፡  ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arba Minch University rolled out a total of 1,475 graduates in its 36th batch 2nd round convocation held at Main Campus Auditorium, on September 23, 2023; 1,348 are undergraduates, 121 are Masters, 3 PGDTs and 3 are PhDs. Click here to see more Photos.

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አውስትራሊያ ሀገር ከሚገኘው ‹‹Menzies School of Health Research›› ከተሰኘ የጤና ምርምር ት/ቤት ጋር በመተባበር በሚያከናውኑት  የጥናት ውጤት ላይ ግምገማዊ ወርክሾፕ መስከረም 8/2016 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ዕጩ ዶ/ር ከበደ ገልገሎ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በእንስሳት ሳይንስ ትምህርት ክፍል በእንስሳት ሥነ-ምግብ/Animal Nutrition/ ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ዕጩ ዶ/ር ከበደ የ3 ዲግሪ የመመረቂያ ጽሑፉን የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት መስከረም 15/2016 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ  በዋናዉ ግቢ አዲሱ አዳራሽ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡