- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማት ማበልጸጊያ ማዕከል ከኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከዩኒቨርሲቲው እና ከአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ለተወጣጡ መምህራን ከግንቦት 04-14/2016 ዓ/ም ተግባር ተኮር የኢንተርፕርነርሽፕ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
Arba Minch University/AMU/ schedules the grand opening of its 600-bedded multi-specialty Teaching and Comprehensive Specialized Hospital so sooner. This state-of-the-art facility marks a significant advancement in healthcare education and research in AMU and quality medical service delivery in the region.
Read more: AMU Inaugurates its Teaching and Comprehensive Specialized Hospital Sooner
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስ እና ሂሳብ ማዕከል (STEM Center) አስተባባሪነት በአርባ ምንጭ ከተማ ከሚገኙ የተመረጡ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችና ከጋሞ ባይራ ሞዴል አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለተወጣጡ ተማሪዎች ፊዚክስ ትምህርትንና ‹‹National Aeronautics and Space Administration/NASA(ናሳ)ን አስመልክቶ ግንቦት 16/2016 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ሥልጠናውን ከናሳ ጆንሰን የሕዋ ማዕከል/ NASA-Johnson Space Center/ የመጡት ዶ/ር ጥላዬ ታደሰ ሰጥተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ፊዚክስ ትምህርትንና ናሳ/NASA/ን አስመልክቶ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበትን 13ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከፌዴራል፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ከልል እና ከጋሞ ዞን አስተዳደር የህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር ‹‹በኅብረት ችለናል›› በሚል መሪ ቃል የአባይ ዘመን ትውልድ የሥነ ጽሑፍ ምሽት ግንቦት 13/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአባይ ዘመን ትውልድ ታላቅ የሥነ ጽሑፍ ምሽት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ት/ክፍል በ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› የትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው የዕጩ ዶ/ር ኢያሱ ጫማ የመመረቂያ ጽሑፍ ግንቦት 13/2016 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉ አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላቱ በአማካሪ ቦርዱ ጸድቋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
ዕጩ ዶ/ር ኢያሱ ጫማ የመጀመሪያ ዲግሪውን በ‹‹Biology›› እና ሁለተኛ ዲግሪውን በ‹‹Dryland Biodiversity›› ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝቷል፡፡ የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› በ2010 ዓ/ም የጀመረው ዕጩ ዶ/ር ኢያሱ የመመረቂያ ምርምሩን ‹‹Plant Communities, Socioeconomic Values, and Carbon Stock Potential of Forest Patches in Wolaita, Southern Ethiopia›› በሚል ርዕስ አከናውኗል፡፡
ዶ/ር ገመዶ ዳሎ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዶ/ር ዳንኤል ፍታሞ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመመረቂያ ጽሑፍ የውጪ ገምጋሚ ሲሆኑ ዶ/ር ሽቴ ጋተው ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ገምጋሚ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ በግምገማ መርሃ ግብሩ የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎችን ጨምሮ የኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የዘርፉ መምህራንና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ታድመዋል፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCAD/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት