
- Details
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ከቱሪዝምና ሆቴል ማኔጅመንት ት/ክፍል ጋር በመተባበር በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት የ2ኛ ዲግሪ ትምህርት ለመክፈት የሚያስችል የውጭ ሥርዓተ-ትምህርት ግምገማ መስከረም 20/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ
Read more: በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት የ2ኛ ዲግሪ ትምህርት ለማስጀመር የውጭ ሥርዓተ-ትምህርት ግምገማ ተካሄደ

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሠለጠናቸውን 5 ሺህ ያህል ተማሪዎች በ3ኛ፣ በ2ኛ እና በመጀመሪያ ዲግሪ መርሃ-ግብሮች መስከረም 29/2014 ዓ.ም በዓባያ ካምፓስ ስቴዲዬም ለ34ኛ ዙር እንዲሁም የሳውላ ካምፓስ ተማሪዎችን መስከረም 30/2014 ዓ.ም በሳውላ ካምፓስ ለ4ኛ ዙር በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሠለጠናቸውን 5 ሺህ ያህል ተማሪዎችን ሊያስመርቅ ነው
- Details
የ4ኛ ዓመት የኤሌክትሪካልና ኮምፕዩተር ምኅንድስና ተማሪዎች ከ2014 ዓ/ም ተመራቂ ባቾች ጋር እኩል እንዲመረቁ ለማድረግ ከሌሎቹ ተማሪዎች ቀድመው ወደ ኢንስቲትዩቱ በመግባት የ2ኛ ሴሚስተር ትምህርታቸውን በመጨረስ ለኢንተርንሺፕ እንዲወጡ ይቻል ዘንድ የፋከልቲው ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት በማድረግ መስከረም 30/2014 ዓ/ም ወደ ካምፓስ እንድትገቡና ከሰኞ ጥቅምት 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

- Details
የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከኢንስቲትዩቱ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር የ2014 ዓ/ም የመጀመሪያ ዙር የምርምር ንድፈ ሃሳብ ግምገማ መስከረም 14/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የ2014 ዓ/ም የምርምር ንድፈ ሃሳብ ተገመገመ

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በጋራ በመሆን በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ፣ ምዕራብ ዓባያ፣ ቁጫ፣ ጨንቻና ገረሴ ወረዳዎች ለማኅበረሰቡ የባዮ-ጋዝ ግንባታ ለማካሄድ መስከረም 4/2014 ዓ/ም የውል ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ በዚህም መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ለሥራ ማስፈፀሚያ 1,875,000 (አንድ ሚሊየን ስምንት መቶ ሰባ አምስት ሺህ) ብር እና የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲሁም ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ 4,054,115 (አራት ሚሊየን ሃምሳ አራት ሺህ አንድ መቶ አሥራ አምስት) ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር የባዮ-ጋዝ ግንባታ ለማካሄድ ስምምነት ተፈራረመ