- Details
የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለተኛ መንፈቀ-ዓመት በመደበኛና በማታ እንዲሁም በሣምንት መጨረሻ መርሐ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡
- Details
ከታኅሣሥ 14/2012 ዓ/ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የተማሪዎች ኅብረት የፓርላማ አባላትና አመራሮች ምርጫ ጥር 03/2012 ዓ/ም የኅብረቱ የሥራ አስፈጻሚ እንዲሁም የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚቴ አባላትን በመምረጥ ተጠናቋል፡፡
በዚህ መሠረት ተማሪ አንዳርጋቸው ደስታ የኅብረቱ ፕሬዝደንት፣ ተማሪ የትምወርቅ ክብሩ ም/ፕሬዝደንት እንዲሁም ተማሪ ቃልኪዳን አባይነህ ዋና ፀሐፊ በመሆን ተመርጠዋል፡፡ በተጨማሪም ተማሪ ገነት ካሳዬ፣ ተማሪ ሀለፎም ደረጀ እና ተማሪ ሚልኪያስ ሙርቴ የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚቴ አባላት ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ
- Details
የዩኒቨርሲቲው የሕክምናና ጤና ሣይንስ ኮሌጅ የማስተማሪያና ሪፌራል ሆስፒታሉን ጨምሮ ቀደም ሲል ከነበረው አደረጃጀት ከፍ ባለ ደረጃ እንዲደራጅ ተጠንቶ ተወስኗል፡፡ በዚህ መሠረት ኮሌጁ በ‹ቺፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር› እንዲመራ የዩኒቨርቲው የሥራ አመራር ቦርድ ታኅሣሥ 10/2012 ዓ/ም ባካሄደው ስብሰባ ወስኗል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ
Read more: ዩኒቨርሲቲው የሕክምናና ጤና ሣይንስ ኮሌጅ የአስተዳደራዊ መዋቅር አደረጃጀት ማሻሻያ አደረገ
- Details
እ.አ.አ ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ ለ4 ዓመታት ሲካሄድ የቆየው የVLIR እንሰት ፕሮጀክት የማጠቃለያ ወርክሾፕ ጥር 12/2012 ዓ/ም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ በፕሮጀክቱ አማካይነት በጋሞ ደጋማ አካባቢዎች በእንሰት አመራረት ሂደትና በእንሰት አጠውላጊ በሽታ ዙሪያ የተደረጉ የምርምር ሥራዎች ቀርበዋል፡፡ በዕለቱ ዩኒቨርሲቲው ከኢትዮጵያ ባዮ-ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባባር የእንሰት ምርት አዘገጃጀትና ድኅረ-ምርት አያያዝን በቴክኖሎጂ ፈጠራዎች የሚያግዝ አዲስ ፕሮጀክትም ይፋ አድርጓል፡፡ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ
Read more: ዩኒቨርሲቲው የእንሰት ምርት አዘገጃጀት፣ ድኅረ-ምርት አያያዝና አጠቃቀም በቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ለማገዝ የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት ይፋ አደረገ
- Details
የዩኒቨርሲቲው የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ትምህርት ክፍል ከዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር በንባብ ክሂሎት ላይ ያተኮረ ፕሮጀክት ቀርፀው በምዕራብ አባያና በልማት 1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለሚገኙ ዝቅተኛ የንባብ ክሂሎት ላላቸው ከ2ኛ - 4ኛ ክፍል ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ የንባብ ክሂሎት ማሻሻያ ትምህርት ለመስጠት የቅድመ መለያ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ፕሮግራሙ ከጥቅምት 1/2012 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን እስከ ሰኔ 30/2012 ዓ/ም እንደሚቆይም ተጠቁሟል፡፡ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ