- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ እና ሶስ ሳህል /SOS Sahel Ethiopia/ ከተሰኙ ግብር ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዞኖች ለተወጣጡ ማኅበራት ተወካዮችና ሥራ አጥ ወጣቶች ለ10 ቀናት የሚቆይ የአሠልጣኞች ሥልጠና ከጥር 29/2016 ዓ/ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል፡፡ ሥልጠናው የእንሰት ተረፈ ምርት ከሆነው ቃጫ ዕሴት የተጨመረባቸውና የተሻለ ዋጋ የሚያወጡ ጌጣጌጦችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማምረት የሚያስችል ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ከእንሰት ቃጫ የተሻለ ዋጋ የሚያወጡ ጌጣጌጦችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማምረት የሚያስችል ሥልጠና እየተሰጠ ነው
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች በአዕምሮ ውቅር ዙሪያ ከየካቲት 4-6/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ለኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች በአዕምሮ ውቅር ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ አዘጋጅነት ከጥር 25/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የዋናው ግቢ ተማሪዎች የእርስ በእርስ እግር ኳስ ውድድር እየተካሄደ ነው፡፡ ውድድሩ በሁለት ምድብ በስድስት ቡድኖች መካከል የሚከናወን ሲሆን በ2016 ዓ/ም ለሚካሄደው የካምፓሶች ውድድር ዋናውን ግቢ የሚወክሉ ተጫዋቾችን ለመለየት ያለመ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ ት/ክፍል በ‹‹Development Economics›› ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ሰሎሞን ከበደ የካቲት 01/2016 ዓ/ም የምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
መቀመጫውን ስዊድን ሀገር ያደረገው ሂዩማን ብሪጅ /HUMAN BRiDGE የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት የሥራ ኃላፊዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታልን የካቲት 01/2016 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የ‹‹HUMAN BRiDGE›› የሥራ ኃላፊዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታልን ጎበኙ