- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና ከጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ለክልሉ ባህልና ቱሪዝም ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት “ቅርሶቻችን ለዘላቂ ልማትና ሀገራዊ ፋይዳ” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ በኢንታጀብልና ኢትኖግራፊ፣ በአርኪዮሎጂ፣ በፓሊዮንቶሎጂና ፓሊዮአንትሮፖሎጂ እንዲሁም ፊሎሎጂ ታሪክና ሥነ-ጽሑፍ ቅርሶች ጥበቃ፣ እንክብካቤና ልማት ዙሪያ ከኅዳር 11-12/2016 ዓ/ም የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: “ቅርሶቻችን ለዘላቂ ልማትና ሀገራዊ ፋይዳ” በሚል መሪ ቃል የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ‹‹ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው፤ በኅብረት እንታገል!›› በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 20ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በተቋም ደረጃ ‹‹የትምህርት ማኅበረሰብ የፀረ ሙስና ንቅናቄ ሳምንት›› በሚል ርዕስ ከኅዳር 11-17/2016 ዓ/ም በሁሉም የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የተለያዩ የሥራ ዘርፍ ቡድን መሪዎች በተገኙበት በማዕከል ደረጃ በፓናል ውይይትና በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ እንደሚደረግና በተመሳሳይ መልኩ በዩኒቨርሲቲው ሳውላ ካምፓስ የሚደረግ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: 20ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እየተከበረ ይገኛል
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥራ ፈጠራ ልማት እና ማበልጸጊያ ማዕከል ከ ‹‹SNV RAYEE›› ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ለአርባ ምንጭ ከተማ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የተዘጋጀውን የቢዝነስ ሃሳብ የመጨረሻ ዙር ውድድር ኅዳር 10/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ ከተማ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የቢዝነስ ሃሳብ የመጨረሻ ዙር ውድድር ተካሄደ
- Details
ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተርነት የቀረቡ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ወ/ሮ ወይንሸት ገ/ጻድቅ (ተ/ፕ)፣ ዶ/ር ዘርይሁን ዘርዶ (ተ/ፕ) እና ዶ/ር ደስታ ጋልቻ (ረ/ፕ) ኅዳር 7/2016 ዓ/ም የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅታቸውን ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት አቅርበው የድምጽ መስጠት ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተርነት የቀረቡ ዕጩ ተወዳዳሪዎች የስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅታቸውን አቀረቡ
- Details
Arba Minch Water Technology Institute offered a basic python for environmental data processing training for staff to enhance research capabilities and promote technological advancements from October to November 2023.Click here to see more photos.
Read more: AWTI offered Basic Python for Environmental Data Processing