- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል አዘጋጅነት በሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች መካከል ሲደረግ የቆየው የ2015 ዓ/ም 2ኛ ዙር የንግድ ሥራ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ሰኔ 16/ 2015 ዓ/ም ተጠናቋል፡፡ በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ስድስት የቢዝነስ ፈጠራ ሃሳቦች ቀርበው ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለወጡ ተወዳዳሪዎች የማበረታቻ ገንዘብ ሽልማት እንዲሁም ለቀሪዎቹ ተወዳዳሪዎች የምስክር ወረቀት ተበርክቷል፡፡ የተሻሻለ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን፣ ዘመናዊ ጡብ ማምረቻ፣ ከአፈር ውጭ ውሃን በመጠቀም የጓሮ አትክልቶችን ማምረትና ከሙዝ ግንድ ወረቀት ማምረት ከቀረቡ የፈጠራ ሥራ ሃሳቦች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ከጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ጋር በመተባበር ከዞኑ 14 ወረዳዎች፣ ስድስት የከተማ አስተዳደሮችና አምስት የግል ማኅበራት ለተወጣጡ የICT እና የቢሮ ማሽን ጥገና ባለሙያዎች ከሰኔ 12- 16/2015 ዓ/ም የቢሮ ማሽን ጥገና ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎክን የመጻሕፍትና መረጃ ማዕከል ከበጎ አድራጎት ማዕከል ጋር በመተባበር በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ ልማት እና አርባ ምንጭ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ ለማረሚያ ብሩህ ተስፋ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ለሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት ከተለያዩ አካላት በልገሳ ያገኟቸውን የመማሪያ ማጣቀሻ መጻሕፍት እና አልባሳት ድጋፍ ግንቦት 22/2015 ዓ/ም አበርክተዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
Arba Minch University Law School students Team wins International Committee of Red Cross, ICRC, National Moot Court Competition on International Humanitarian Law held in Addis Ababa from May 29-30/2023. Click here to see the Pictures!
- Details
በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በኮምፒውቲንግና ሶፍትዌር ኢንጂነርንግ ፋከልቲ በ “Computing and Information Technology” ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር መሳይ ሳሙኤል ሰኔ 02/2015 ዓ/ም ከሰዓት በኋላ ከ8፡30 ጀምሮ የ3ኛ ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዋናዉ ግቢ መግቢያ አካባቢ በሚገኘው አዳራሽ ያቀርባል፡፡