- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በኮቪድ-19 ዙሪያ በተሠሩ 28 ምርምሮች ላይ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ታኅሣሥ 22/2014 ዓ.ም ግምገማዊ ወርክሾፕ አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በጥናትና ምርምር ተደግፎ ለኢትዮጵያውያን ሕጻናት፣ መምህራንና ወላጆች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ንባብ ክሂል ለመማሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን “Easy Ways to Read in English” ወይም “የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፍኖተ-ንባብ” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ታኅሣሥ 26/2014 ዓ/ም ከጧቱ 02፡30 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት፣ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ት/ክፍል መምህራን፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ የጋሞ ዞንና በዞኑ የሚገኙ ወረዳዎች የትምህርት ሴክተር ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ መግቢያ በር አካባቢ በሚገኘው አዳራሽ የውይይትና የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ይካሄዳል፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል የፍትሕ እና የሕግ ምርምርና ሥልጠና ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የሕግ ት/ቤቶች ማኅበር ጋር በመተባበር ‹‹Contemporary Challenges, Trends and Governance of Internally Displaced Persons Protection in Ethiopia›› በሚል ርዕስ 2ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ አካሂዷል፡፡ በጉባዔው ከተለያዩ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት በመጡ ምሁራን ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት 2ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ አካሄደ
- Details
የሕግ ት/ቤት በሽግግር ፍትሕ አማራጮች ያለፉ ጉዳዮች መፍታት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ የዩኒቨርሲቲው ሕግ ተማሪዎች፣ መምህራንና ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የተወጣጡ ግለሰቦች በተገኙበት ታኅሣሥ 12/2014 ዓ/ም ሴሚናር አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር 28ኛው ሀገር አቀፍ ኮንፍራንስ ላይ ከቀረቡ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶች ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቅ ሀና እንዳሻውና በማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ ሁሴን አሊ የላቀ የመመረቂያ ጽሑፍ በማቅረብ ታኅሣሥ 9/2014 ዓ/ም ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
Read more: በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር ኮንፍራንስ 2 የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን በላቀ የመመረቂያ ጽሑፍ ተሸላሚ ሆኑ