- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲው ሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ከሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ከ6ቱ ካምፓሶች የተለያዩ ሥራ ክፍሎች ለተወጣጡ አስተባባሪዎች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ከየካቲት 01-02/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው የአእምሮ ዕውቀት፣ የስሜት ልህቀት፣ ስብእናና ተፈጥሯዊ ባህሪያት በስፋት ተዳሰዋል፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የሆቴልና ቱሪዝም ማኔጅመንት ት/ክፍል የ2ኛ ዓመት ተማሪ የነበረችው ጽጌረዳ ግርማይ በቅርብ ጓደኛዋ ተማሪ በደረሰባት የስለት ጥቃት ጥር 23/2014 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷን አስመልክቶ በኮሌጁ አስተባባሪነት የካቲት 01/2014 ዓ/ም የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡
Read more: የተማሪ ጽጌረዳ ግርማይን ኅልፈተ ሕይወት አስመልክቶ የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ
- Details
የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ጋር በመተባበር በፍትሐብሔር አሠራር ማኑዋል፣ በግንባታ ውሎች፣ በፍርድ ቤት ሥልጣን፣ በክስ አቀራረብና መስማት ሂደት እና በመጥሪያ አደራረስ ላይ በክልሉ ከሚገኙ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ዐቃቤያን ሕግ ከጥር 28-29/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
Read more: በደቡብ ክልል ከሚገኙ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ዐቃቤያን ሕግ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ዲግሪ ነባር የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች ከየካቲት 14-19/2014 ዓ.ም ድረስ ቲቶሪያል የሚሰጥ ስለሆነ በየካምፓሶቻችሁ ተገኝታችሁ ገለጻውን እንድትከታተሉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ነባር የክረምት መርሃ -ግብር ተማሪዎች በሙሉ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕወሓት ወራሪ ኃይል ከፍተኛ ጉዳት ላጋጠመው ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር ሥራ የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ወረቀቶች፣ ካኪ ፖስታዎች፣ እስክሪብቶዎች፣ ቾክ፣ የቢሮና የተማሪ ወንበሮች፣ የማስተማሪያ ጠረጴዛዎች፣ ለተማሪ የምግብ አገልግሎት የሚውሉ የካፍቴሪያ ዕቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ፕላስቲክ ጋኖች፣ የእንጀራ ምጣዶች፣ የፍራሽ፣ የዕቃ ማመላለሻ ጋሪዎችና የመሳሰሉ ቁሳቁሶችን ጥር 21 እና 22/2014 ዓ.ም በወልድያ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ድጋፍ አድርጓል፡፡ የቁሳቁስ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 2.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለወልድያ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዙር የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ