የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል በደቡብ ኦሞ ዞን በተለይም በሙርሲ አካባቢ የቪሰራል ሌሽማኒያሲስ/Visceral Leishmaniasis/ በሽታ ተጠቂዎች ቁጥር ማሻቀብን ተከትሎ የምርመራ ናሙና ለሚወስዱ ሐኪሞችና ወረርሽን መከሰት አለመከሰቱን ለማረጋገጥ ዳሰሳ ለሚያካሂዱ ከዞኑ ወረዳዎችና ከጂንካ ከተማ ለተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የካቲት 25/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ


127ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ‹‹ዝክረ ዓድዋ ድል ለብሔራዊ መግባባት›› በሚል መሪ ቃል ያለፈውን ታሪክ በመዘከር፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጸና እና የሀገር ግንባታን በሚያጠናክር መንፈስ የካቲት 23/2015 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የ12 ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial Program/ ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉትን ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በግል ከፍሎ ለመማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

በ2014 የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው ለአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ትምህርት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቅበላ ቀን የካቲት 29/2015 ዓ/ም፣ የምዝገባ ቀን የካቲት 30 እና መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን መጋቢት 04 ቀን 2015 ዓ.ም ይሆናል፡፡ ስለሆነም የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ትምህርት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን ወደዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡-   

 

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ‹‹የ21ው ክፍለ ዘመን በአፍሪካ የኢትዮጵያ ስትራቴጂ/Ethiopia’s Africa Strategy for Twenty-first Century›› በሚል ርዕስ የፖሊሲ የምክክር መድረክ የካቲት 17/2015 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡