በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ‹‹Water Resource and Irrigation Engineering›› ፋከልቲ በ‹‹Irrigation and Drainage Engineering›› ትምህርት ፕሮግራም ላላፉት አምስት ዓመታት የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር አበራ ሽጉጤ የምርምር ሥራውን ነሐሴ 26/2015 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አቶ ታምራት ኃይሌ ከአባታቸው ከአቶ ኃይሌ ገበየሁ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወላንሳ ተፈራ በቀድሞው ወሎ ክፍለ ሀገር ተንታ አካባቢ ሚያዝያ 10/1980 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከ“Jhpiego Ethiopia Health Workforce Improvement Program” ጋር በመተባበር በደቡብ ኢትዮጵያ ለሚገኙ አምስት የጤና ሳይንስ ፕሮግራም ያሏቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፡- አርባ ምንጭ፣ ሀዋሳ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ዋቸሞና ወልቂጤ እንዲሁም የአርባ ምንጭ እና ፋርማ የጤና  ሳይንስ ኮሌጆች ዓመታዊ የጤና ሳይንስ ትምህርት ጥራት ግምገማ ከነሐሴ 26-27/2015 ዓ/ም ድረስ አካሂዷል፡፡ ተጫማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን ለሚገኙ ነርሶች፣ ጤና መኮንኖች፣ ሐኪሞችና የላቦራቶሪ ባለሙያዎች በቁንጭር (Cutaneous Leishmaniasis)ና ሌሎች የቆዳ በሽታዎች ዙሪያ ከነሐሴ 24/2015 ዓ/ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በ2012 እና 2013 የትምህርት ዘመን ባጋጠመን የኮቪድ-19 (ኮሮና ቫይረስ) ወረርሽን ምክንያት መደበኛ የትምህርት ካላንደር መዛባቱ ይታወቃል፡፡ በወረርሽኙ ምክንያት የተከሰተውን የትምህርት ጊዜ ብክነት በማስተካከል ላይ የምንገኝ በመሆኑ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2013 ባች (3 ዓመት ቅድመ ምረቃ) ተማሪዎች ቅበላ፣ ምዝገባ እና ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በልዩ ሁኔታ በጊዜ እንዲሆን ተወስኗል፡፡