በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ትምህርት መስኮች የ3 ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የስምንት 3 ዲግሪ ተማሪዎች መመረቂያ ጽሑፎች ከሰኔ 19-21/2016 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡ የ8ቱም ዕጩ ዶክተሮች መመረቂያ ጽሑፎች አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላታቸው በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝተው ጸድቀዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ በ2016 ዓ/ም የ12ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አሰጣጥ፣ አስተዳደርና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ጉዳዩ ከሚመልከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ሰኔ 21/2016 ዓ/ም የውይይት መድረክ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሠለጠናቸውን ከ2,500 በላይ የቅድመና ድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ሰኔ 26/2016 ዓ.ም በጎፋ ሳውላ ከተማ ሳውላ ካምፓስ እና ሰኔ 27/2016 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ አባያ ካምፓስ ያስመርቃል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ባለፉት 36 ዙር ምረቃዎች ከ82,000 በላይ ብቃት ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ለሀገራችን ልማትና እድገት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ያለ አንጋፋ ተቋም ነው፡፡

የ2016 ትምህርት ዘመን ማጠቃለያ የወላጆች ቀን በ30/10/2016 ዓ.ም. እሁድ ቀን ከጧቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ በዋና ግቢ ቴክኖሎጂ ትልቁ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ ስለሆነም የት/ቤታችን ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በተባለዉ ቀን፣ ሰዓትና ቦታ እንድትገኙ እያሳሰብን በዕለቱ የተማሪዎች የዓመቱ ሥራ ውጤት መግለጫ ካርድ የሚሰጥ፣ ለቀጣይ ትምህርት ዘመን አቅጣጫ የሚቀመጥበት ውይይት የሚካሄድበትና ውሳኔ የሚተላለፍበት እንዲሁም ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች የሚሸለሙ ስለሆነም ሁላችሁም ተገኘታችሁ እንድትታደሙ እንገልጻለን፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ የ2015/16 የሥራ ዘመን መጠናቀቁን ተክትሎ ለ2017/18 ለሁለት ዓመታት የሚያገለግሉ አዲስ የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ሥራ አስፈፃሚ አባላት ምርጫ ሰኔ 18/2016 ዓ.ም ተጠናቋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡