- Details
በዘንድሮው 39ኛ ዙር የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ በሕክምና (Medicine) ጨምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ (First Degree)፣ በሁለተኛ ዲግሪ (Masters) እና በዶክትሬት ዲግሪ (PhD) ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ይመረቃሉ።
ዩኒቨርሲቲው የተመራቂ ተማሪዎችን የስኬት ጉዞ ለመዘከርና ታላቁን የምረቃ በዓል በታቀደው መሠረት ለማካሄድ የሚያስችሉትን አስፈላጊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እያጠናቀቀ ይገኛል። በዕለቱም የተመራቂ ቤተሰቦች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶችና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በተገኙበት ደማቅ ሥነ-ሥርዓት እንደሚከናወን ይጠበቃል።
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፤ ለመላው ተመራቂዎች፣ ለተመራቂ ቤተሰቦችና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ! እያለ መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል!
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጀርመን ዓለም አቀፍ ትብብር ድርጅት (GIZ) እና ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ - ቱርካና ድንበር ተሻጋሪ ቀጠና የሚታዩ የፍልሰት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የግጭት ቅነሳ እና የሰዎች ዝውውር ችግሮች ላይ ያተኮረ የምርምር ማረጋገጫ (Validation) ወርክሾፕ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በኃይሌ ሪዞርት አካሂዷል። ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር በድንበር ተሻጋሪ ፍልሰትና አየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደ
- Details
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምግብ ዋስትናን ለማሻሻል፣ የገጠር ነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ከፍ ለማድረግ፣ ሴቶችን በምጣኔ ሀብት (ኢኮኖሚ) ለማብቃት እና የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን ለመገንባት ያለመው ታላቅ የግብርና ልማት ፕሮጀክት በአርባ ምንጭ ከተማ በተካሄደ የምክክር መድረክ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ ጀምሯል። ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የገጠር ነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ያለመው የ"ሺ-ፈራ (ሞሪንጋ)" ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ
- Details
ARBA MINCH, ETHIOPIA – June 16, 2026 – Arba Minch University (AMU) hosted a high-level scientific seminar featuring Dr. Lawrence Banks, Director-General of the International Centre for Genetic Engineering and Biotechnology (ICGEB), bringing together university leaders, researchers, academic staff, postgraduate students, and grant beneficiaries to explore opportunities for international research collaboration, scientific mobility, and biotechnology innovation. Click here to see more photos.
Read more: Dr. Lawrence Banks Delivers High-Level Scientific Seminar at Arba Minch University
- Details
Dr. Lawrence Banks, Director-General of the International Centre for Genetic Engineering and Biotechnology, conducted a series of visits to research facilities and innovation sites at Arba Minch University from June 14–15, 2026, as part of his official visit to Ethiopia, highlighting the achievements of the long-standing partnership between the two institutions in biotechnology research, innovation, and sustainable development. Click here to see more photos.
- AMU Hosts Continental Workshop on Machine Learning, Optimization and Applications
- CALL FOR APPLICATIONS: SHORT COURSE TRAINING FOR PHD STUDENTS
- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) ንጋት ሃይቅ የውሃ ውስጥ የመሬት አቀማመጥ (Bathymetric Survey) የመጀመሪያ ምዕራፍ ካርታ ርክክብ በታላቅ ድምቀት ተከናወነ
- በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው የሁለት ወራት የአመራር ሥልጠና ተጠናቀቀ


