- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ ከተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በካምባ ወረዳ ዲንጋሞ ቀበሌ ማይጸሌ ወንዝ ላይ የሚያስገነባው አነስተኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ የዲዛይንና ቅድመ ጥናት ሥራ ዙሪያ የክርስቲያን ኤይድ ኢትዮጵያ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፕሮጀክቱ አባላትና አማካሪ ቦርድ አባላት በተገኙበት ነሐሴ 25/2014 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን/The United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR) ቢሮ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በተፈናቃይ ሰዎች የሕግ ጥበቃ፣ በሴቶችና ሕፃናት መብት ጥበቃ፣ በንብረት ሕግ እንዲሁም በካምፓላ ስምምነት ዙሪያ በአሌ ልዩ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ 17 ቀበሌያት ለተወጣጡ የማኅበራዊ፣ የወረዳና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ መርማሪ ፖሊሶች፣ የፍትሕ ቢሮ ዐቃቤያን ሕግ እንዲሁም ከሴቶችና ሕፃናት እና ከልዩ ወረዳው ምክር ቤት ለተወጣጡ 30 ሠልጣኞች ከነሐሴ 30 - ጳጉሜ 1/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በሴቶችና ሕፃናት መብት ጥበቃ እና በንብረት አያያዝና አስተዳደር ላይ ያተኮረ የሕግ ግንዛቤ ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስና እና ሒሳብ /Science, Technology, Engineering & Maths – STEM/ ማዕከል ከዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ ጉድኝትና ከተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬቶች እንዲሁም ከ ‹‹STEM Power›› መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ከጋሞ፣ ጎፋና ኮንሶ ዞኖች እና ከደራሼ፣ ባስኬቶ፣ ቡርጂና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 291 ከ7ኛ- 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ሒሣብ፣ ኤሌክትሮኒክስና ICT ትምህርቶች ከሐምሌ 15 - ነሐሴ 28/2014 ዓ/ም ሲሰጥ የቆየውን የሥልጠና መርሃ ግብር አጠናቋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በ"STEM" ማዕከል ከ7ኛ- 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ሲሰጥ የቆየው የሥልጠና መርሃ ግብር ተጠናቀቀ