አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የሕግ ት/ቤት እንዲሁም የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና የሳውላ ካምፓስ ተማሪዎችን እንዲሁም በሁሉም ኮሌጆችና ፕሮግራሞች በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን ተማሪዎች ሐሙስ ሐምሌ 13/2015 ዓ/ም በዋናው ግቢ አዲሱ አዳራሽ እና ዓርብ ሐምሌ 14/2015 ዓ/ም በሳውላ ካምፓስ  በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ ይሆናል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 7/2015 ዓ/ም ድረስ ሲሰጥ የነበረው የ2015 ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና/Exit –Exam/ በስኬት ተጠናቀቀ፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

‹‹ነገን ዛሬ እንትከል!›› በሚል መሪ ቃል 5ኛው ዙር ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 10/2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ ሁሉንም የዩኒቨርሲቲውንና የአካባቢውን ማኅበረሰብ በማሳተፍ ይጀመራል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለ2015 ዓ/ም ዕጩ ተመራቂ የኮሚዩኒኬሽንና ኮምፒውተር ምኅንድስና ተማሪዎች እንዲሁም ለኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ምኅንድስና መምህራን ‹‹5G and 3GPP Radio Access Network and Evolution of 3Gpp Based Radio Access Network (RAN) for Mobile Communication›› በሚል ርእስ ሰኔ 29/2015 ዓ/ም ትምህርታዊ ሴሚናር አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ