
- Details
የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ከትምህርት ሚኒስቴርና ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከወልቂጤ፣ ወራቤ፣ ዋቸሞ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ጂንካ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ለመጡ የግዥና ንብረት እና የፋይናንስና በጀት አስተዳደር ኃላፊዎች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች፣ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ክፍል ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የተማሪዎች አገልግሎት ኃላፊዎች፣ የግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ሌሎች የሚመለከተቸው አካላት ሙስናን መከላከልና መቆጣጠርን አስመልክቶ ከታኅሣሥ 05 - 06/2016 ዓ/ም የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመጡ የተለያዩ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የፀረ ሙስና ሥልጠና ተሰጠ

- Details
18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት”በሚል ሀገራዊ መሪ ቃል የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ ት/ቤት የአስተዳደር ኃላፊዎችን ጨምሮ ርዕሰ መምህራን፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ታኅሣሥ 05/2016 ዓ.ም በድምቀት ተከብሯል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: 18ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት ተከበረ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ፈረንሳይ ሀገር ከሚገኝ ‹‹Fund for Innovative Development (FID)›› ድርጅት ጋር በመተባበር በሚያከናውነው ‹‹Adoption of Rhizobium Inoculant Technology (ARIT)›› የተሰኘ የትብብር ፕሮጀክት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ‹‹Bio-Fertilizer›› ማምረት ላይ የለውጥ ማሳያ (Progress) ሪፖርትና የመስክ ምልከታ ታኅሣሥ 4/2016 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የተፈጥሮ ማዳበሪያ ‹‹Bio-Fertilizer›› ማምረት ላይ ያተኮረ የትብብር ፕሮጀክት የለውጥ ማሳያ ሪፖርትና የመስክ ምልከታ ተካሄደ

- Details
Arba Minch University along-with the Ethiopian English Language Professionals’ Association will be hosting the Ethiopian English Language Professionals’ Association/EELPA/ South Chapter Launching workshop in AMU on 23rd December, 2023, at Main Campus.

- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዕድሜያቸው ከ10-19 ዓመት በሆኑ አፍላ ወጣቶች ዲጂታል ሄልዝ አገልግሎትን በመጠቀም የፀረ ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት አወሳሰድን ማሻሻል ላይ በማተኮር የተከናወነ የምርምር ሥራን አስመልክቶ ታኅሣሥ 6/2016 ዓ/ም የምርምር ማስተዋወቂያ ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ የምርምር ሥራው በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የማኅብረሰብ ጤና ት/ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም ስዊድን ሀገር በሚገኘው ለንድ ዩኒቨርሲቲ/Lund University/ የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪ ዓባይነህ ቱንጄ የተሠራ ነው፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ቴክኖሎጂን መጠቀም የፀረ ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት አወሳሰድን ለማሻሻል እንደሚረዳ ያረጋገጠ ጥናት ይፋ ሆነ
- An International Workshop on Bioinformatics and Mathematical Modeling of Infectious Diseases held in Arba Minch University
- ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመጡ የግዥና ንብረት እንዲሁም የፋይናንስና በጀት አስተዳዳር ኃላፊዎች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ሥልጠና እየተሰጠ ነው
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን በተሰጠው ግብረ መልስና ሌሎች ተያያዥ ተቋማዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከመኅበረሰቡ ውይይት እያካሄደ ይገኛል
- ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች አገልግሎት የሚውል የኮምፒውተር ድጋፍ ተበረከተ