- Details
አቶ ሰለሞን ንጉሤ ከአባታቸው አቶ ንጉሤ ጨሬ እና ከእናታቸው ወ/ሮ እቴነሽ ተሾመ በአርባ ምንጭ ከተማ በ1979 ዓ/ም ተወለዱ፡፡
አቶ ሰለሞን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ዞን በኩልፎ መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ያጠናቀቁ ሲሆን በመቀጠልም ከግንቦት 10/2001 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 24/2002 ዓ.ም በአሌልቱ ፖሊስ ማሠልጠኛ ት/ቤት በ22ኛ ዙር መደበኛ የፖሊስነት ሙያ ሥልጠና አጠናቀው የምስክር ወረቀት አግኝተዋል፡፡
- Details
አቶ ግርማ ታደሰ ከአባታቸው አቶ ታደሰ መርቼ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ወለቱ ሙንዶ በ1980 ዓ/ም በባስኬቶ ልዩ ወረዳ ዶኮ አይማ ቀበሌ ተወለዱ፡፡
አቶ ግርማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ ልማት ሙሉ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመደበኛው እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በማታው ፕሮግራም ተከታትለው አጠናቀዋል፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስነትምህርትና ስነባህሪ ሳይንስ ት/ቤት ለዩኒቨርሲቲው ተደራሽ በሆኑ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በሚገኙ ት/ቤቶች የትምህርት ስኬቶችና ተግዳሮቶች ዙሪያ የትምህርቱ ዘርፍ ባላድርሻዎች ምክክር እና የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻል ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ታላቅ የምርምር ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ጥር 20/2015 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድርጅቱና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሰባት ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች በተገኙበት ጥር 20/2015 ዓ/ም ዓመታዊ ጉባዔውን በአርባ ምንጭ ፓራዳይዝ ሎጅ አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡