- Details
በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ አመራር ዝግጅት ምልመላና ስምሪት ሥርዓት ማስተግበሪያ መመሪያ መሠረት በዩኒቨርሲቲው ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ቦታ በተደረገው ግልጽ ውድድር መሠረት የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ከታኅሣሥ 22/2015 ዓ/ም ጀምሮ ዶ/ር ቦጋለ ገብረማርያም የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ሆነው እንዲያገለግሉ የኃላፊነት ሹመት ሰጥቷል፡፡
Read more: ዶ/ር ቦጋለ ገብረማርያም የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ
- Details
The editorial board of OMO International Journal of Sciences would like to invite researchers, experts, academia, and entrepreneurs to submit manuscripts of original research, review articles, technical notes and short communications for publication in the journal. OMO Int. J. Sci. is Arba Minch University based journal which publishes top-level research works from all areas of Natural, Computational, Agricultural, Veterinary, Food, Medical and Health Sciences.
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በጎፋና ኮንሶ ዞኖች እና በደራሼ ልዩ ወረዳ በዝናብ እጥረት በተከሰተ ድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የሚውል 2.1 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የምግብ እህል ድጋፍ ከታኅሣሥ 26-28/2015 ዓ/ም በየሥፍራዎቹ በመገኘት አስረክቧል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ በጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት ት/ክፍል በ‹‹ Disaster Risk Management›› ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር አሸናፊ ኃይሉ ሐሙስ ጥር 04/2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ የመመረቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዋናዉ ግቢ መሰብሰቢያ አዳራሽ ያቀርባል፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የኢኮኖሚክስ ት/ክፍል በ ‹‹Development Economics›› ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ኤዞ ኤማኮ ማክሰኞ ታኅሣሥ 25/2015 ዓ/ም የምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡